ሙሴ ጸሊም ኢትዮጵያዊ: እናትና አባቱ ፀሓይ ያመልኩ ነበረ:: ኃጥያት በሠራ ጊዜ "ተው አምላካችን ፀሓይ ይጣላሃል " ይሉት ነበረ::"ፀሓይማ አምላክ ቢሆን እስከዛሬ ባቃጠለኝ " ይላቸው ነበር:: አንድ ቀን እውነተኛውን የፀሓይ አምላክ ማወቅ ብችል ብሎ ተመኘ:: መንፈስ ቅዱስ አነሳስቶት ወደ ገዳመ አስቄጥስ (ግብጽ )ገባ:: በገዳመ አስቄጥስ የነበረ አንድ ካህን አይቶት "ሊፈጀን የመጣ ነው " ብሎ አሰበ:: እርሱ ግን ሄዶ "አምላክ ማነው አስተምረኝ " አለው:: ካህኑም ከመምህር ኤስድሮስ አገናኘው:: አስተማረው አጠመቀው ማዕረገ ምንኩስናንም ሰጠው::
40 ዘመን ከሰው ተለይቶ በዓት ዘግቶ በጸሎት ኖረ:: በኍዋላም በ 500 መነኮሳት ላይ ተሾመ ቀን ቀን ሲያስተምር ይውላል:: ለሊት ለሊት በረሃ ወርዶ እንጨት ሰብሮ ውኃ ቀድቶ በየደጃፋቸውላይ አኑሮላቸው ያድራል:: እነርሱ ግን ማን እንደሚያመጣላቸው አያውቁም ነበር:: አንድ ቀን ሰይጣን ይህን መልካም አገልግሎቱን ለማስተው እንጨት ሰብሮ ውኃ ቀድቶ ሲመጣ እግሩን በድንጋይ መትቶታል:: ሙሴ ግን የሰይጣን ጸብ መሆኑ ስለገባው ይበልጥ በአገልግሎቱ ጸና እንጂ አልተንበረከከም::
40 ዘመን ከሰው ተለይቶ በዓት ዘግቶ በጸሎት ኖረ:: በኍዋላም በ 500 መነኮሳት ላይ ተሾመ ቀን ቀን ሲያስተምር ይውላል:: ለሊት ለሊት በረሃ ወርዶ እንጨት ሰብሮ ውኃ ቀድቶ በየደጃፋቸውላይ አኑሮላቸው ያድራል:: እነርሱ ግን ማን እንደሚያመጣላቸው አያውቁም ነበር:: አንድ ቀን ሰይጣን ይህን መልካም አገልግሎቱን ለማስተው እንጨት ሰብሮ ውኃ ቀድቶ ሲመጣ እግሩን በድንጋይ መትቶታል:: ሙሴ ግን የሰይጣን ጸብ መሆኑ ስለገባው ይበልጥ በአገልግሎቱ ጸና እንጂ አልተንበረከከም::
በአል በሚያደርጉበት ጊዜ "አባታችን ማዕረገ ምንኩስና ተቀብለህ ናዝዘን" ብለው ወደ ሊቀጳጳስ ይዘውት ሄዱ ሊቀጳጳሱ ግን ባየው ጊዜ "እንዲህ ያለውን ጠቋራ ታመጡብኛላችሁን ?" ብሎ ናቀው:: ሙሴም "ገጽህ የከፋደግ አደረጉብህ " እያለ ራሱን እየገሰፀ ወጣ:: እመቤታችንም ተገልጻ ሊቀጳጳሱን ገስጻውልቡ ንጹሕ አይደለምን ?" አለችው:: ሊቀጳጳሱም ተጸጽቶ አስጠርቶ ሾመው::
ከዚህ በኋላ ከደቀመዛሙርቱ 7ቱን አስከትሎ ወደ አባ መቃርስ ሄዶ ሳለ በርበር (ሽፍቶች ) ገዳሙን ሊያቃጥሉ እነርሱንም ሊገድሉ መጡ:: እሱም ለደቀመዛሙርቱ "ከእናንተ የፈራ ይሽሽ "አለ:: "አባታችን አንተስ አትሸሽምን? " አሉት :: እርሱ ግን "ሰማዕትነትን ጠልቼ እሸሻለሁን ?" አለ :: ደግሞም በወጣትነቱ የሌላ ሰው ደም አፍስሶ ነበርና እንደንስሓ እንዲሆነው ሰማዕትነትን ፊት ለፊትተጋፈጠ በዚያም አንገቱን ሰጠ :: እርሱን ባዩ ጊዜ 6ቱ ደቀመዛሙርት አንገታቸውን ለሰይፍ እየሰጡ ዐርፈዋል :: ሰባተኛው መነኮስ ግን ፈርቶ ጢሻ ውስጥ ተደብቆ ነበር:: ሙሴና 6ቱ መነኮሳት ከተሰየፉ በኋላ መልአከ እግዚአብሔር 8 አክሊላትን ይዞ ወርዶ 7ቱን ለነርሱ አቀዳጅቶ አንዱ በእጁ ሲቀር አየው:: ከተደበቀበት ወጥቶ አንገቱን በመስጠት የርሱ ድርሻ የሆነችውን አክሊል ሳታመልጠው አግኝቷታል::
ግብጾች በሙሴ ጸሊም ስም ቤተክርስቲያን አንጸው ገድሉን አጽፈው እስከዛሬ ይዘክሩታል ያስታውሱታል:: በቅርቡም ታሪኩን የሚያሳይ ፊልም ሠርተው ለእይታ አብቅተዋል::
በረከቱ ረድኤቱ በእኛ ላይ ይደር !
የሃይማኖት አጋሮቻችንን ከዘረኝነት መንፈስ ውጪ የምናይበትን የሙሴ ጸሊምንና የግብጻውያኑ መነኮሳትን ዓይነት ልቦና እግዚአብሔር ያድለን ! አሜን !
0 comments:
Post a Comment
አስተያየት ወይም መልዕክት ካልዎት፤ ከዚህ በታች ያለውን ሰሌዳ ይጠቀሙ።