May 8, 2011

ጊዮርጊስ ዘጣና


ጊዮርጊስ ዘጣና  የተባለው ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አባቱ ምግባረ ሃይማኖት እናቱ ዓመተ ማሕጸን ይባላሉ። ጻድቁ በጥቅምት ፳፯ ቀን ተወለደ ። ሀገሩ ጣና ዘጌ ሲሆን በምናኔ ዓለማት የኖረ በዋሻ ውስጥ ውኃ እየፈለቀለት ይመገብና ይጠጣ የነበረ ነው። ከእለታት አንድ ቀን መልአክ መጥቶ "አባ  ሁሉ ሆኖልሃል። ነገር ግን አንድ ነገር ይቀርሃል " አለው። እሱም "ምንድነው ?" ብሎ ጠየቀ መልአኩም "ምን ቢመነኩሱና ጸሎተኛ ቢሆኑ ምን ለጋስ ደግ ቢሆኑ ምን ሊቅና አዋቂ ቢሆኑ ሥጋውንና ደሙን ካልተቀበሉ መጽደቅ የለምና ሄደህ ተቀበል " አለው
ጻድቁም ተነስቶ ከዋሻው ወጥቶ ወደ ቤተክርስቲያን ሄዶ ገብቶ በጸሎተ ሐሙስ እለት ቆሞ ሲያስቀድስ ሊቀ ጳጳሱ ቅዳሴ ገብቶ "ሀበነ " ሲል ዐሥሩም ጣቶቹ በደም ሲነከሩ አየ ደነገጠ ! ቀድሞ ጌታን ሲያየው የነበረው በሌላ መልክ ነበረና አሁን ግን የሊቀ ጳጳሱ እጅ በደም ሲነከር ጌታ እንደተሰቀለ ሆኖ በመንበሩ ቆሞ ደሙ ሲፈስ በማየቱ ደንግጦ ከመሬት ላይ ወድቆ ከቤተመቅደሱ በራፍ ላይ ሳይንቀሳቀስ 40 ዘመን እንደአንድ ደቂቃ ሆኖለት ኖሯል በመጨረሻም በ94ዓመቱ በመጋቢት 27 ቀን ዐርፏል በሞተም ጊዜ  መቃብሩን ተኩላ ቆፍሮ መነኮሳቱ ቀብረውታል በስሙ የተሠራውም ታቦት በጣና ይገኛል

ለአባታችን ከተገለጸለት የጌታ የነገረ -መስቀሉ ፍቅር ለእኛም ትንሽ ብልጭታው ይብራልን ! በረከቱ ረድኤቱ በእኛ ላይ ይደርብን ! አሜን !

0 comments:

Post a Comment

አስተያየት ወይም መልዕክት ካልዎት፤ ከዚህ በታች ያለውን ሰሌዳ ይጠቀሙ።