May 4, 2011

አቡነ መዝሙር ድንግል

አቡነ መዝሙር ድንግል የተባለው ኢትዮጵያዊ ጻድቅ ትውልዱ ጎጃም ሲሆን ፤ የቤተክርስቲያናችን ባለውለታ ነው። ይህ ጻድቅ በታህሳስ 12 ቀን በጎጃም ሞጣ አማኑኤል ተወለደ። የመነኮሰውም በታኅሳስ 12 ቀን ነው። በመነኮሰ በ ዓመቱም በታኅሳስ 12 ቀን ተሾመ። ይህ ጻድቅ በ ሊቃውንት እየተመራ : 4ቱን ወንጌላት በግዕዝ በእብራይስጥ በአረማይክ በአረብ ቋንቋ በ ዓመት ውስጥ ያጻፈ ሲሆን ባለ ዓምድ ነበር። ዛሬ ይህ መጽሐፍ በአንድ ገዳምውስጥ ይገኛል በስሙ በጎጃም እነሴ ገዳም አለው
ከዚህም ሌላ ነገረ ማርያምን በግዕዝና በእብራይስጥ ያጻፈ ይህ ጻድቅ ሲሆን ደራሲም ፀሓፊም ጸሎተኛም ባህታዊም ሁሉን የያዘ አባት ነው። እረፍቱም በሰኔ 11 ነው። በክብራን ገብርኤልምተቀብሯል

ረድኤቱ በረከቱ በሁላችን ላይ ይደር አሜን 

1 comments:

አስተያየት ወይም መልዕክት ካልዎት፤ ከዚህ በታች ያለውን ሰሌዳ ይጠቀሙ።