Feb 28, 2014

የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት ፦ ቅድስት

ምንጭ፡መዝገበ ታሪክ ቁጥር 2
የዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሳምንት ቅድስት ይባላል፡፡ የሰንበትን ቅድስና የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡ በተጨማሪ ቅድስት የተባለበት ምክንያት 40 ቀን የጌታችን ጾም የሚጀምርበት ሳምንት ስለሆነ ቅድስት ጾሙን ለማዘከር ቅድስት ተብሏል፡፡ ‹‹የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ›› ዘጸ. 208 ይህንን ቃለ እግዚአብሔር በሊቀ ነቢያት ሙሴ ላይ አድሮ ተናግሯል፡፡ ዕረፉባት  ያለው እግዚአብሔር የፍጥረቱን አቅም ባሕሪ ስለሚያውቅ ነው፡፡ ስናከብር ለነፍስ ዕረፍትና ፍስሐን ለሥጋ በረከት ሊያሰጡ የሚችሉ ሃይማኖታዊ ተግባራትን በመፈጸም የሚከበር ነው፡፡ በቤተክርስቲያን በመሰብሰብ ቃለ እግዚአብሔርን በመስማት/በመማር/ ንስሓ ገብቶ ቅዱስ ቁርባን በመቀበል፣ የተጣላ በማስታረቅ፣ ያዘነ የተከዘ በማረጋጋት በማጽናናት የታሰረ በመጠየቅ፣ በችግር የወደቁትን በመጎብኘት በአጠቃላይ በማቴ. 2535-37 ላይ የተጠቀሱትን ምግባራት በመፈጸም ከተከበረ ከእግዚአብሔር ዘንድ የማያልቅ ዘላለማዊ በረከትን ያስገኛል፡፡ ኢሳ. 564-8 ይህችንም ዕለተ ሰንበት ያላከበረ እንዲገደል ትእዛዝ ተሠርቶ ነበር፡፡ እግዚአብሔርም ለሙሴ ‹‹ለእናንተ ቅዱስ ነውና ሰንበትን ጠብቁ፤ የሚያረክሰውም ሁሉ ፈጽሞ ይገደል÷ ሥራንም በእርሱ የሠራ ሰው ሁሉ ከሕዝቡ መካከል ተለይቶ ይጥፋ፡፡ . . . ››ዘጸ. 3114-15 ይህችን ዕለት የናቁ ሰዎች በሞት ተቀጥተዋልና፡፡ ዘኁ. 1532-36

የዕለተ ሰንበት ክብር

  1. በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ፍጥረታትን ፈጥሮ በዕለተ ሰንበት ከሥራው ሁሉ ዐርፎባታል፡፡ ዘፍ. 23 ዘጸ. 208
  2. በሐዲስ ኪዳን ጌታችን የተፀነሰባት፣ ትንሣኤውን የገለጠባት፣ ለሐዋርያት ጸጋ መንፈስ ቅዱስን የሰጠባት፣ ዳግመኛ ለፍርድ የሚመጣባት . . . ወዘተ በመሆኗ ነው፡፡ በአጠቃላይ ታላላቅ ሥራዎችን የሠራባት በመሆኗ ከሌሎች ቀናት ለይተን እናከብራታለን፡፡
  3. ሌሎች ቀናት ሲያልፉ ዕለተ ሰንበት ባለማለፏ ለዘላለም ጸንታ በመኖሯ ነው፡፡ ድርሳነ ሰንበት ምዕ. 183-7 በዕለተ ምጽአት ከማያልፉ ነገሮች መካከል ቃሉ፣ ዕለተ ሰንበት፣ የሰው ልጅ ነው፡፡

ዛሬ ዛሬ የኃጢአት ሥራ ሁሉ ቀን ተለይቶ የሚፈጸመው ዝሙቱ፣ ሴሰኝነቱ፣ መዳራቱ ወዘተ . . . በዚች  ቅድስት ዕለት ሆኗል፡፡ ‹‹ይህን ኃጢአት ቅድስት በምትሆን በዕለተ ሰንበት፣ በሰሙነ ሕማማት የሚፈጽም ወዮለት›› ይላል /ፍትሐ ነገሥት/ የባልና የሚስት ሩካቤ ኃጢአት ባይሆንም በማይገባ ወቅት ይልቁንም በዕለተ ሰንበት፣ በሰሙነ ሕማማት፣ ረቡዕ እና ዓርብ ከተፈጸመ ኃጢአት ነው፡፡ ኢሳ. 5813-14 ‹‹ፈቃድህን በተቀደሰው ቀኔ ከማድረግ እግርህን በሰንበት ብትመልስ የሰንበትም ደስታ እግዚአብሔር የቀደሰው ክቡር ብትለው የገዛ መንገድህን ከማግኘት ከንቱ ነገርንም ከመናገር ተከልክለህ ብታከብረው በዚያን ጊዜ በእግዚአብሔር ደስ ይልሃል በምድር ከፍታዎችም ላይ አወጣሃለው፡፡ የአባትህን የያዕቆብን ርስት አበላሃለሁ የእግዚኣብሔር አፍ ተናግሮአልና›› ሮሜ. 146 ‹‹ቀንን የሚያከብር ለእግዚአብሔር ብሎ ያከብራል›› በማክበራችን ከእግዚአብሔር የምንቀበለው ዘላለማዊ ዋጋ ክብር አለና፡፡ ባለ ማክበራችን ደግሞ ቅጣት ጉዳት አለውና ነው፡፡ ሰንበትን በሚገባ እንድናከብር ቸሩ አምላካችን እግዚአብሔር ይርዳን፡፡ አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር። 

0 comments:

Post a Comment

አስተያየት ወይም መልዕክት ካልዎት፤ ከዚህ በታች ያለውን ሰሌዳ ይጠቀሙ።